አሁን ልጆችዎ በአማርኛ ቋንቋ የ “መጽሐፍ ቅዱስ ለልጆች” መተግበሪያ ተሞክሮን ሊያገኙ ይችላሉ!

መጽሐፍ ቅዱስ  ለልጆች

ዛሬ ከአጋራችን OneHope ጋር በመሆን ፣ የ ”መጽሐፍ ቅዱስ ለልጆች” መተግበሪያ በአማርኛ ቋንቋ መጀመሩን ስናሳውቅ በደስታ ነው ፡፡ አሁን ከመቼውም በበለጠ ብዙ ልጆች በራሳቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ተሞክሮ የመደሰት እድል አላቸው ፡፡

ቋንቋዎችን መቀያየር ቀላል ነው ፣ በመተግበሪያው ቅንብሮች ውስጥ ይገኛል

  1. መተግበሪያዎን በቅርብ ጊዜ ወደተለቀቀው ማዘመንዎን ያረጋግጡ።
  2. መተግበሪያውን ክፈት እናየጊር አዶ ይጫኑ (ጊር አዶ) ለመክፈትቅንብሮች.
  3. ቋንቋን ይጫኑ እና የሚፈልጉትን ይምረጡ ፡፡

ድምጹ አሁን በዚያ ቋንቋ ይጫወታል ፣ እና ማንኛውም ጽሑፍ በዚያ ቋንቋም ይታያል!

እባክዎን ይህንን ታላቅ ዜና ለማክበር ያግዙን!

ፌስቡክፌስቡክ ላይ ያጋሩ

ትዊተርትዊተር ላይ ያጋሩ

ኢሜይልበኢሜይል በኩል ያጋሩ


መጽሐፍ ቅዱስ  ለልጆች እየሱስ

ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ለልጆች

OneHope ጋር በመተባበር የቀረበው, የመጽሐፍ ቅዱስ ለልጆች መተግበሪያ ከYouVersion, የ መጽሐፍ ቅዱስ መተግበሪያ ሰሪዎች ነው። ልጆች በራሳቸው አስደሳች የሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ተሞክሮን እንዲያገኙ የተቀየሰ ሲሆን፤ መጽሐፍ ቅዱስ ለልጆች በሚሊዮን 65 የአፕል፣ የአንድሮይድ እና የኪንድል መሳሪያዎች ላይ ተጭኗል።ሁልጊዜም ሙሉ በሙሉ ነፃ ነው። አሁን በመላው ዓለም ላይ የሚገኙ ልጆች በ62 ቋንቋዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ለልጆች መተግበሪያ እየተደሰቱ ነው — አሁን በአማርኛ ቋንቋም ጭምር!

App Store Google Play Amazon

መዝሙር 91 – የእግዚአብሔር ጥበቃ

1  
በልዑል መጠጊያ የሚኖር፣ ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ሥር ያድራል።

2  
እግዚአብሔርን፣ “መጠጊያዬ፣ ምሽጌ፣ የምታመንብህ አምላኬ” እለዋለሁ።

3  
እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ፣ ከአሰቃቂ ቸነፈር ያድንሃልና።

4  
በላባዎቹ ይጋርድሃል፤ በክንፎቹ ሥር መሸሸጊያ ታገኛለህ፤ ታማኝነቱ ጋሻና መከታ ይሆንሃል።

5  
የሌሊትን አስደንጋጭነት፣ በቀን የሚወረወረውንም ፍላጻ አትፈራም፤

6  
በጨለማ የሚያደባ ቸነፈር፣ በቀትር ረፍራፊውም አያሠጋህም።

7  
በአጠገብህ ሺህ፣ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃል፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም።

8  
በዐይንህ ብቻ ትመለከታለህ፤ የክፉዎችንም መቀጣት ታያለህ።

9  
እግዚአብሔርን መሸሸጊያ፣ ልዑልንም መጠጊያህ አድርገኸዋልና።

10  
ክፉ ነገር አያገኝህም፤ መቅሠፍትም ወደ ድንኳንህ አይገባም፤

11  
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ፣ መላእክቱን ስለ አንተ ያዛቸዋልና።

12  
እግርህ ከድንጋይ ጋር እንዳይጋጭ፣ በእጆቻቸው ወደ ላይ ያነሡሃል።

13  
በአንበሳና በእፉኝት ላይ ትጫማለህ፤ ደቦሉን አንበሳና ዘንዶውን ትረግጣለህ።

14  
“ወዶኛልና እታደገዋለሁ፤ ስሜን አውቆአልና እከልለዋለሁ።

15  
ይጠራኛል፤ እመልስለታለሁ፤ በመከራው ጊዜ ከእርሱ ጋር እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ፤ አከብረዋለሁ።

16  
ረጅም ዕድሜን አጠግበዋለሁ፤ ማዳኔንም አሳየዋለሁ።”

መዝሙር 91

Psalm 91 in English

የእግዚአብሔር ጦር ዕቃ

ኤፌሶን 6:10-18

10  
በተረፈ በጌታና ብርቱ በሆነው ኀይሉ ጠንክሩ።

11  
የዲያብሎስን የተንኰል ሥራ መቋቋም ትችሉ ዘንድ፣ የእግዚአብሔርን ሙሉ የጦር ዕቃ ልበሱ።

12  
ምክንያቱም ተጋድሎአችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን ከዚህ ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ ከሥልጣናትና ከኀይላት እንዲሁም በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሳን መናፍስት ሰራዊት ጋር ነው።

13  
ክፉው ቀን ሲመጣ መቋቋም ትችሉ ዘንድ የእግዚአብሔርን ሙሉ የጦር ዕቃ ልበሱ፤ ሁሉን ከፈጸማችሁ በኋላ ጸንታችሁ መቆም ትችላላችሁና።

14  
እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ዝናር ታጥቃችሁ፣ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፣

15  
በሰላም ወንጌል ዝግጁነት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ።

16  
ከእነዚህም ሁሉ ጋር፣ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤

17  
የመዳንን ራስ ቊር አድርጉ፤ የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።

18  
በሁሉ ዐይነት ጸሎትና ልመና፣ በማንኛውም ሁኔታ በመንፈስ ጸልዩ፤ ይህንም በማሰብ ንቁ፤ ስለ ቅዱሳንም ሁሉ በትጋት ልመና አቅርቡ።

Ephesians 6 in Amharic

Ephesians 6 in English

ፍቅር ታጋሽ ነው፤ ደግሞም ቸር ነው። 

ፍቅር ታጋሽ ነው፤ ደግሞም ቸር ነው። 

4  
ፍቅር ታጋሽ ነው፤ ደግሞም ቸር ነው። ፍቅር አይመቀኝም፤ አይመካም፤ አይታ በይም፤

5  
ተገቢ ያልሆነ ነገር አያደርግም፤ ራስ ወዳድ አይደለም፤ አይበሳጭም፣ በደልን አይቈጥርም።

6  
ፍቅር ከእውነት ጋር እንጂ በዐመፅ ደስ አይሰኝም።

7  
ፍቅር ሁል ጊዜ ይታገሣል፤ ሁል ጊዜ ያምናል፤ ሁል ጊዜ ተስፋ ያደርጋል፤ ሁል ጊዜ ጸንቶ ይቆማል።

8  
ፍቅር ከቶ አይወድቅም፤ ነገር ግን ትንቢት ቢሆን ይሻራል፤ ልሳንም ቢሆን ይቀራል፤ ዕውቀትም ቢሆን ይሻራል።

9  
ምክንያቱም የምናውቀው በከፊል ነው፤ ትንቢት የምን ናገረውም በከፊል ነው።

10  
ነገር ግን ፍጹም የሆነው ሲመጣ በከፊል የነበረው ይሻራል።

11  
ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እናገር ነበር፤ እንደ ልጅ ዐስብ ነበር፤ እንደ ልጅም አሰላ ነበር። ከጐለመስሁ በኋላ ግን የልጅነትን ነገር እርግፍ አድርጌ ትቻለሁ።

12  
አሁን የምናየው በመስተዋት ውስጥ እንደሚታይ በድንግዝግዝ ነው፤ በዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን። አሁን የማውቀው በከፊል ነው፤ በዚያን ጊዜ እኔ ራሴ ሙሉ በሙሉ የታወቅሁትን ያህል ዐውቃለሁ።

13  
እንግዲህ እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከእነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው።

1 Corinthians 13 in Amharic

1 Corinthians 13 in English

ገና መጽሐፍ በስተኋላ

ገና መጽሐፍ በስተኋላ

“አንቺ ግን፣ ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፤ ከይሁዳ ነገዶች መካከል ትንሿ ብትሆኚም፣ አመጣጡ ከጥንት፣ ከቀድሞ ዘመን የሆነ፣ የእስራኤል ገዥ፣ ከአንቺ ይወጣልኛል።”

ሚክያስ 5:2

ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፤ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም ዐማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።

ኢሳይያስ 7:14

በዚህ ሐሳብ ሳለ፣ የጌታ መልአክ በሕልም ተገለጠለት፤ እንዲህም አለው፤ “የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፤ ዕጮኛህን ማርያምን ወደ ቤትህ ለመውሰድ አትፍራ፤ የፀነሰችው በመንፈስ ቅዱስ ነውና። ወንድ ልጅ ትወልዳለች፤ ስሙንም ኢየሱስ ብለህ ትጠራዋለህ፤ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልና።”

ማቴዎስ 1:20-21

“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወድዷልና።

ዮሐንስ 3:16

ሕፃን ተወልዶልናል፤ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል። ስሙም፣ ድንቅ መካር፣ ኀያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም ልዑል ይባላል።

ኢሳይያስ 9:6

ቃልም ሥጋ ሆነ፤ በመካከላችንም ዐደረ፤ እኛም ጸጋንና እውነትን ተሞልቶ ከአባቱ ዘንድ የመጣውን የአንድያ ልጅን ክብር አየን።

ዮሐንስ 1:14

ነገር ግን የተወሰነው ዘመን በደረሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን፣ ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤ ይህም የሆነው የልጅነትን መብት እናገኝ ዘንድ ከሕግ በታች ያሉትን ለመዋጀት ነው።

ገላትያ 4:4-5

መልአኩ ግን እንዲህ አላቸው፤ “አትፍሩ፤ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች አምጥቼላችኋለሁና። ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋልና፤ እርሱም ጌታ ክርስቶስ ነው።

ሉቃስ 2:10-11

ድንገትም ብዙ የሰማይ ሰራዊት ከመልአኩ ጋር ታዩ፤ እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ፣ እንዲህ አሉ፤ “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም፣ ሰላምም እርሱ ለሚወድዳቸው ሰዎች በምድር ይሁን!”

ሉቃስ 2:13-14

ጠቢባኑ ንጉሡ ያለውን ከሰሙ በኋላ ጕዟቸውን ቀጠሉ። ይህም በምሥራቅ ያዩት ኮከብ እየመራቸው ሕፃኑ እስካለበት ድረስ ወሰዳቸው። ኮከቡንም ሲያዩ ከመጠን በላይ ተደሰቱ። ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩ፤ ተንበርክከውም ሰገዱለት። ሣጥኖቻቸውን ከፍተው ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤም አቀረቡለት። እግዚአብሔርም ወደ ሄሮድስ እንዳይመለሱ በሕልም ባስጠነቀቃቸው መሠረት፣ መንገድ አሳብረው ወደ አገራቸው ተመለሱ።

ማቴዎስ 2:9-12